Telegram Group Search
#የሊባኖሷ_ሙሽራ

በመጀመርያ በክንፍ ላይ ስሎ ለመላእክት ሲገልጣት የጠባቂነት መዓረግን መስጠቱ ነበርና ከማኅፀን ጀምሮ እንዲጠብቃት አደራ በተሰጠው መልአክ በኩል እንደተናገረው በዘመድ በኩል ቢሆንም ቅሉ ለምትወለደዋ ሕፃን ዘመዶቿ የሰማይ መላእክት  ነበሩና በእነርሱ ተከባ ወደ ምትወልድበት ስፍራ እንዲሄዱ ተነገራቸው ።

እራሷ ከዓለም አይደለችምና በመወለዷ በቤት ውስጥ የነበሩ ሰዎች ዓለማዊ ተድላ ደስታን እንዳያደርጉ በመንፈሳዊያን ዘመዶቾ በመላእክት ታጅባ ከቤት ወጣች ። ከቤቱ ወጥቶ ሕገ እግዚአብሔርን ስቶ የነበረ አዳምን የሚፈልግ ጌታ እናቱ ናትና ከቤት ወጥታ ቀድሞ አባቶቿ ነብያት እርሷን በራዕይ ወደ ተመለከቱበት ታላቅ  ስፍ ወደ ሊባኖስ ተራራ ተጓዘች ። በሊባኖስ ተራራ ጉያ ስር በእንበሶች ጉድጓድ እንደምትወለድ ትንቢት የተነገረላት የሊባኖስ ሙሽራ እርሷ ናትና ።

ከጉሩማኑ አናብስት ከነዳዊት ከነሰሎሞን ፤ ከተላላቁ ተራሮች ከነ አብርሃም ፣ ይስሐቅ ፣ ያዕቆብ አብራክ የተገኘችው እመቤታችን ሰው በማይኖርበት ስፍራ ልትወለድ ተወሰነ። በዚያም ሳሉ ክብሯ ከአድባራት ሁሉ በላይ የሆነ ከቀደሙትም ከኋለኞቹም በላይ ስሟ የገነነ ፣ ከፀሐይ ይልቅ የምትደምቅ እመቤታችን በግንቦት አንድ ቀን ተወለደች ።

እሷ የሁሉ ፍጥረት ናት እንጅ የሐናና የኢያቄብ ብቻ ባለመሆኗ በአንድ ሰው ቤት ውስጥ እንዳትወለድ መንፈስ ቅዱስ ከለከለ ።

     ( ሕይወተ ማርያም ገጽ 85-87 ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ )

አማላጅነቷ የእናትነት ፍቅሯ ይጠብቀን ።

http://www.tg-me.com/ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ/com.ortodoxtewahedo
💚💛❤️💚💛❤️💚💛❤️💚

📖ዳግም ትንሣኤ

📖ዳግም ትንሣኤ ለምን ተባለ?

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ሰሙነ ሕማማትና ሰሙነ ትንሣኤን እንድናከብር ቀደም ሲል በዲዲስቅልያ ኋላም በፍትሐ ነገሥት ታዝዟል፡፡

“እስመ ሰሙነ ዐብይ ሰሙነ ሕማማት እንተ ትተልዋሄ ሰሙነ ትንሣኤ ወዘይትፈቀድ ከመ ናእምር እስመ ዘሐመ
ናሁ ትንሣአ” ሲል ይገኛል፡፡
ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 19 ፤

የሰሙነ ትንሣኤ መጨረሻው ስምንተኛው ቀን ዳግም ትንሣኤ ነው፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተነሣው አንድ ጊዜ ነው፡፡ ዳግም ትንሣኤ ለምን ተባለ?

📖ዳግም ትንሣኤ የተባለበት

ምክንያት፡- በአከባበር፥በሥርዓት የመጀመሪያውን ትንሣኤ ስለሚመስል ነው፡፡የትንሣኤ ዕለት የሚባለው ቃለ እግዚአብሔር ሳይለወጥ፤በሙሉ በዚህ ቀን ይደገማል፡፡ ከዚህም ሌላ ሁለት
መጠሪያ ስሞች አሉት፡፡ እነዚህም “ፈጸምን አግብዓተ ግብር” ይባላሉ፡፡ “ፈጸምነ” የተባለበትም፤ ሰሙነ ትንሣኤ በዓል አክብረን ፈጸምን ማለት ነው፡፡ “አግብዓተ ግብር” የተባለበትም፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “አባ ወአቡየ ግብር ዘወሀብከኒ ፈጸምኩ… እኔ ልሠራው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር ላይ አከበርሁህ” ያለውን ከቅዳሴ በኋላ ሊቃውንት በዚህ ቀን ስለሚዘምሩት ነው፡፡
ዮሐንስ 7፥4

በተጨማሪም የሐዋርያው ቶማስ ምስክርነት የሚታሰብበት ነው፡፡ ዳግመኛ ከስምንት ቀን በኋላ ደቀ መዛሙርቱ በዝግ ቤት ሳሉ፥ ቶማስም ከእነርሱ ጋር ሳለ ደጁም ተዘግቶ ሳለ፥ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቶ በመካከላቸው ቁሞ እንዴት ሰነበታችሁ አስታረቅኋችሁ” አላቸው፡፡ ሁለት ሰዓት አሳልፎ ስለመጣ “እምድኅረ ሰሙነ” አለ እንጅ፥ በስምንተኛው ቀን ሲል ነው፡፡ በመጀመሪያው መገለጡ ያልተገኘው ሐዋርያው ቶማስ ትንሣኤውን አላመነም ነበርና፤ “ጣትህን ወደዚህ አምጣ እጆቼንም እይ፤ እመን እንጅ ተጠራጣሪ አትሁን” አለው፡፡ ቶማስም መለሰ “ጌታዬ አምላኬ ሆይ” አለ፡፡ መዳሰሱን ሲያይ “ጌታዬ”፤መቃጠሉን ሲያይ “አምላኬ ሆይ “አለ፡፡ ገቦ መለኮቱን የዳሰሰች እጁ ሕያዊት ሁና፤ (በሕይወት ትኖራለች)
በሕንድ አገር ከታቦት ጋር በመንበሩ ላይ ያስቀምጧታል፡፡
በዓመት በዓመት በእምቤታችን በዓል በአስተርእዮ ሊያጥኑ ሲገቡ፥ የሚሾመውን ወጥታ ቀኝ እጁን ትይዘዋለች ዓመት አገልግሎ ያርፋል፤ እንዲሁ በዓመቱ የሚሾመውን ተራምዳ ትይዘዋለች፤ እንዲህ እያለች ትኖራለች፡፡

ይህም የሚያስተምረን የጌታን ተአምራት፤ የሐዋርውን ሥልጣንና
ብቃት ነው፡፡ጌታም ቶማስ ሆይ! ብታየኝ አመንክን? ሳያዩኝ የሚያምንብኝ ብፁዓን ናቸው አለው፡፡ ዮሐ 21፥24–29

ለብርሀነ ትንሣኤው ያደረሰን አምላካችን፥ፍጻሜ ሕይወታችን በሃይማኖት የቀናን፤ በምግባር የጸናን
ያድርገን! አሜን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር

http://www.tg-me.com/ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ/com.ortodoxtewahedo

💚💛❤️💚💛💚💛❤️💚💛
Audio
መልካሙ ዘመን ደረሰ
ቅዱስ ያሬድ

Size:-12.4MB
Length:-54:32

በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ

http://www.tg-me.com/ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ/com.ortodoxtewahedo
http://www.tg-me.com/ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ/com.ortodoxtewahedo
Audio
በታላቅ ኃይል ተነሣ

Size:-12.4MB
Length:-1:16:39

    በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ


http://www.tg-me.com/ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ/com.ortodoxtewahedo
http://www.tg-me.com/ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ/com.ortodoxtewahedo
የቅድስት ሥላሴ ስዕል እንዴት ይሳላል  በአምሳለ አረጋዊ  ስለምን  ይሳላሉ?

በውስጥ  ብዙዎቻችሁ  በጠየቃችሁት  መሰርት  የቀረበ 

ቅድስት  ሥላሴ ሲሳሉ  በስም በአካል በግብር ሦስት መሆናቸውን  በአገዛዝ  በስልጣን አንድ መሆናቸው መገለጥ አለበት ፡፡ አንድነታቸውን  ለማመልከት በኪሩቤል  መንበር  ላይ እንደተቀመጡ ያለ ቅደም ተከተል (ፊትና ዋላ ከላይ  ወደታች  ሳይሆን )አንድ አይነት  አስተያየትና አቀማመጥ ተቀምጠው  ልብሳቸው  ወይም  ቀሚሳቸው አንድ ላይ  ሳይነጣጠል (ለየብቻው  ሳይሆን )በአንድ አይነት  ቀለም  ይሳላል። መንበር  የስልጣን  የአገዛዝ የመንግስት  ምሳሌ ሲሆን  በአንድ  መንበር  መቀመጣቸውም  በስልጣን  በአገዛዝ   አንድ መሆናቸውን  ያምለክታል። ተቀምጠው መሳላቸው በሁሉቦታ ያለ በሁሉ የነገሰ (ንጉሰ ነገስት እግዚአ አጋእዝት) መሆኑን ለመግለጽ ነው ።
ያለቅደም  ተከተል  መቀመጣቸውም  በቅድምና  አንድ  መሆናቸውን  ያሳያል።

 ሦስትነታችውን  ለመግለጥ አለምን  በግራ እጃቸው እንደያዙ በቀኝ እጃቸው ሲባርኩ(ጠቋሚ ጣት  ወደላይ  ቀጥ  ብሎ  ከመሃል ጣት  እስከ ትንሽ ጣት ያሉት ሦስት  ጣቶች  ታጥፈው )ያሦስቱም  ፊት ወደ አንድ አቅጣጫ  ሆኖ  ወደ አንድ አቅጣጫ  የሚያይ ሆኖ  አካላዊ  ገጽታቸውም  እኩል በተመጣጠነ  የልብሳቸውም  ከውስጥና እና ከውጭ መጎናጸፊያቸው  ቀይ ተደርጎ ይሳላል  ::
ሲሣሉም  በአምሳለ አረጋዊ መሆን አለበት።ይህም ዘላለማዊነታቸውን  በሁሉቦታ  መኖራቸውን  ታጋሽነታቸውን  ፈራጅነታቸውን  አስተዋይነታቸውን  ለመግለጥ ነው።የምድር ነግስታት ያልፋሉ  እሱግን  የተለየ የማያልፍ  መነሻውም  መድረሻውም የማይታወቅ  መሆኑን  ለመግለጥ በአምሳለ አርጋዊ ይሳላሉ

ዳን 7፥9  ዙፋኖችህም  እስኪዘረጉ ድረስ አየው  በዘመናትም የሸመገለው ተቀመጠ እንዲል

 ከዚህ  በተጫማሪ በዙፋናቸው  ዙሪያ በአራቱ  መዕዘናት  አራቱ እንስሳት ባለስድስት ክንፍ ሆነው በገጸ አንበሳና  በገጸ ላህም  በገጸ ሰብ እና በገጸ ንስር  በሁለት  ክንፎቻቸው  እጃቸውን ሸፍነው  በሁለት ክንፋቸው እግሮችቸውን ሸፍነው  በሁለት  ክንፋቸው  ደሞ ቀኝ እና ግራ ዘርግተው ይሳላሉ ። ሃያራቱ ካህናትም  ልብሰተክኖ ለብሰው  በእጃቸውም እጣን  የሞላበት የወርቅ መዕጠንት ይዘው  አንድም  አክሊላችውን   ከራሳቸው  አውርደው  በዙፋኑ ፊት ሲሰግዱ  መሳል አለበት።
ለወዳጆ ያካፍሉ

http://www.tg-me.com/ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ/com.ortodoxtewahedo
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን !!!

እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ወርሃዊ መታሰቢያ  እንዲሁም ለሌሎች ቅዱሳን መታሰቢያ በዓል  በሰላም በጤና አደረሳችሁ፤ አደረሰን።

የአብርሐምን ቤት የባረኩ ሥላሴ እኛንም በህይወታችን በኑሮዋጭን በአገልግሎታችን  በትዳርአችን በትምርታችን በሥራችን ይባርኩን ።

ሥሉስ ቅዱስ ለሚታምን ሁሉ እምነትን በረከትን ሀገራችን ኢትዮጽያን ሰላም ያድርጉልን አሜን ::

     #መልካም ቀን

  #ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
   ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉 
@ortodoxtewahedo
የጣፈጠ #ህይወትን ይፈልጋሉ?

አንተ ልዩ ሆነህ የተፈጠርከው በእግዚአብሔር  ፈቃድ ነውና ምንም ሳታማርር ህይወትህን ኑራት።
#ባለህ_እየታመንኽ ህይወትህን አጣፍጣት። #ሰዎችን_ለመምሰልና_የነሱ_ግልባጭ_ለመሆን_አትጣር
 የአንተ ንጹህና እጹብ ድንቅ ያልታየ ማንነት የሚወጣው በራስህ
#መተማመን፣መኩራትና እራስህን ማክበር ስትጀምር ነውና። በዙሪያህ ምንም አይነት ዝነኞች ትልቅና ልዩ ተሰጦ ያላቸው ሰዎች ቢኖሩም በአንተ ውስጥ ያለው ልዩ ስጦታ ግን ከሁሉም ይለያል! ይልቃል! ይበልጣል! እነዚህ ልዩ ያልካቸው ሰዎች በአፈጣጠራቸው የተለዩ ሆነው ሳይሆን ይህንን ምስጢር ስላወቁትና ስለተገበሩት ብቻ ነው ከሌሎች ተለይተው አሁን ያሉበት የደረሱት። አንተም እንደነሱ የደረሱበት እንደውም ከነሱበላይ መስጠት መስራትና ማበርከት ከፈለክ ወደ እኔ ጠጋ በልና ጆሮህን ስጠኝ እኔም ሚስጢሩን ሹክ ልበልህ።

 ተጠጋኸኝ ልጀምር? "

#እራስህን_ሁን! #እራስህን_አክብር! #እራስህን_ውደድ!" #እራስህን_እንደማትወደው_እንደማታከብረውና_እንደማትሆነው_ስታስብ_ከማይመረመረው_ከእግዚአብሔር _እውቀትጋር_እየተደራደርክ_ነውና_ሁለቴ አስብ። ሰዎች ከሚሉህ በላይም እግዚአብሔር ሲፈጥርህም ምክንያት አለውና የሌለህን ትተህ ያለህን ዋጋ ስጥ። በሌለህ ነገር ስለምታገኘው ሳይሆን ባለህ ነገር ስለምትለውጠው ተመራመር። በሌለህና ባልተጨበጠው ነገር ትልቅ ነገር ለመስጠት ከማሰብ ይልቅ ባለህ ነገር ትንሽ ነገር ለመስጠት ሞክር። ያኔ አንተ ውስጥ የተደበቀው ከሌሎች የተለየው ድንቅ ፍልቃቂ ማበብ ይጀምራል። ብርሃንህ በዓለም ሁሉ ይሰፋል። ስምህም በሰዎች ልብ ውስጥ ይነግሳል። በምድር ላይ በኖርክበት ዘመን ሁሉ ዘመንህ የጣፈጠ ይሆንልሀል።

👉 ለመቀላቀል

👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
http://www.tg-me.com/ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ/com.ortodoxtewahedo
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
“ደግሞም ኢየሱስ፦ እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም ብሎ ተናገራቸው።”

— ዮሐንስ 8፥12

http://www.tg-me.com/ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ/com.ortodoxtewahedo
#ፍትህ ለሊቁ

ይህ ዘመን የቤተ ክርስትያን የስደት ዘመን ነው ።
ያለ ጥፋት ያሰሩሀል የፈለጉትን የሚደረግበት ሊቁ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ ከታሰረ 13 ቀን ሆነው ።
ኦርቶዶክስ መሆን ወንጀል ነው ?????

http://www.tg-me.com/ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንወቅ/com.ortodoxtewahedo
መላእክት ምስጋናቸው እረፍታቸው ፣እረፍታቸው ምስጋናቸው ሆኖ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ እግዚአብሔርን ያለማቋረጥ ያመሰግናሉ፡፡

ቤተክርስቲያንም አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ናትና ይህን አብነት በማድረግ ልዑል እግዚአብሔር ሃያ አራት ሰዓት የሚመሰገንበትን የምስጋና ሥርዓት ዘርግታለች፡፡

ሕያው እግዚአብሔር የአዳም ልጆች በመላእክት ምስጋና
እንዲያመሰግኑት በመውደዱ ሰማያዊውን ምስጋና ይማር
ዘንድ ቅዱስ ያሬድን መረጠ፡፡

ማህሌታዊው ቅዱስ ያሬድ የመላእክት የምስጋናውን እንጀራ
ያበላን የቤተ ክርስቲያን ባለውለታ እንቁ ነው።

በረከቱ ይደርብን!

< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >

#መልካም ቀን

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
#ሰንበተ ክርስትያን

እሑድ ማለት"አሐደ" ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን ትርጉሙ የመጀመሪያ እንደማለት ነው። ይኽች ዕለት በመጽሐፍ ቅዱስ "ከሳምንቱ በፊተኛው ቀን " በመባል ትታወቃለች።

ዮሐንስም በራዕዩ "የጌታ ቀን" ያላት ናት
(ራዕይ 1፥10)

ቅዱስ ያሬድም በድጓው ላይ "ዕለተ እግዚአብሔር" የሚላት ዕለተ እሑድ ናት።

መልካም ዕለተ ሰንበት ይኹንልን

#መልካም ቀን

#ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉
@ortodoxtewahedo
2024/06/25 22:27:40
Back to Top
HTML Embed Code: